የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ስርዓተ ቀብር ክብራቸውን በሚመጥን መልኩ እንዲፈፀም ያደረጉ አካላትን አመሰገነ ።
ታላቁ ዐሊም ህልፈታቸው ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ የሽኝት ስነስርዐቱ እና ሌሎች ተጠባቂ መርሃግብሮች የሁላችንም አባት የሀገር ምልክት የሆኑትን ዐሊም ክብራቸውን እንዲሁም እስላማዊ አደቡ ተጠብቆ እንዲፈፀም በተለያየ መንገድ አስተዋፅኦ የነበራቸውን አካላት እንደሚያመሰግን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል ። በተለይም ለኢፌድሪ ፕሬዚዳንት ለጠቅላይ ሚኒስቴር ፣ለሰላም ሚኒስቴር ፣ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር፣ለአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ፥ለሃይማኖት

